Monthly Archives: August 2012

ኦርቶዶክሳውያን ድረ-ገጾችን ለማዘጋት እየተዶለተላቸው ይገኛል

(አንድ አድርገን ሐምሌ 25 ፤ 2005 ዓ.ም)፡- ዘመኑን ዋጁ እንዲል ቃሉ ከጊዜ ወዲህ ድረ-ገፆች መረጃን ለምዕመናን እያስተላለፉ ይገኛሉ ፤ የአምስት ዓመት እድሜ ያስቆጠረችው በእድሜ አንጋፋዋ “ደጀ ሰላም”ን ጨምሮ ፤ አንድ ዓመት በቅጡ ያልሞላት “አንድ አድርገን” ፤ ደቂቀ ናቡቴና አሐቲ ተዋህዶን የመሰሉ ገጾች የቤተክርስትያንን መረጃዎች የመናፍቃንን አካሄዶች በየጊዜው በማውጣት ይታወቃሉ ፤ ከዚህ በተቃራኒ በሌላኛው ጎራ የቆሙ የተሀድሶያውያን እና የመናፍቃን ገጾች ያለመታከት ቤተክርስትያኒቱን ለመከፋል ያለ እረፍት እየሰሩ ይገኛሉ ፤ “አባ ሰላማ”ና አውደ ምህረትን የመሰሉት ገጾች ውስጥ በሚገኙ እነሱን ከሚመስሏቸው ሰዎች ጋር በመሆን መረጃዎችን እየተቀባበሉ ምንፍቅናቸውን እና ኢ-ኦርቶዶክሳዊ የሆነ አካሄዳቸውን በጽሁፋቸው እየገለጹ ይገኛሉ ፤ የነዚህን ገጾች ጽሁፍ አይቶ እነ ማን እንደሆኑ ለማወቅ የተለየ ብልሀትን የጠለቀ ምርመራ ማድረግን አይጠይቅም ፤ ቅዱሳንን የሚዘልፉና  ገድላትን የሚያንቋሽሹ ጽሁፎቻቸው ምስክሮቻቸው ናቸው፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ደጀ-ሰላም እና አንድ አድርገን በኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይነበቡ ቢደረግም እነዚህን የመሰሉ የተሃድሶያውያን ገጾችን ግን የደረሰባቸው የለም ፤ አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ ከወደ አሜሪካ እነዚህን ገጾች እንዲታገዱ የሚጠይቅ ስብሰባ መደረጉን የአቋም መግለጫ መውጣቱን የሚያመላቱ መረጃዎች ወጥተዋል ፤ ከበስተጀር እየተዶለተላቸው ይገኛል ፤ እነርሱ አልገባቸውም እንጂ “አንድ አድርገን” እና “ደጀ ሰላም” በፌስ ቡክ ካልሆነ በስተቀር በቀጥታ የማይነበቡበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል ፤ አንድ አድርገን በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አሁን ለ3ተኛ ጊዜ እክል ገጥሟታል ፤ ከዚህ በፊት አንድ በአንድ እየተባለ ሁለት ገጾች ቢዘጉም አሁን ግን በተለዋጭነት መረጃ ለማስተላለፍ የምትተቀምባቸው 6 ገጾች በጠቅላላ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይሰሩ ተደርገዋል ፤ ይህ ሁሉ ቢሆንም ከኢትዮጵያ ውጭ በቀን ቢያንስ በሺህ በሚቆጠሩ ሰዎች እንደምትጎበኝ የብሎጉ ስታተስ ይጠቁማል ፤ ከቀናት በኋላም እነርሱ መዝጋት ካልሰለቻቸው እኛ መክፈቱ ስለማይከብደን ተጨማሪ አማራጭ ገጾች እንደምንከፍት በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

እንደ “አንድ አድርገን” እምነት ካለው ተጨባጭ ሁኔታ በመነሳት የተሃድሶያውያን እና የመናፍቃንን አካሄድ መረጃዎች ሰዎች ዘንድ አድርሰናል ብለን አናምንም ፤ እስከ አሁን ከወጣው መረጃ እየሰበሰብንና እያጠናከር ያሉ ጉዳዮች ይበዛሉ ፤ የሐዋሳው ጉዳይ ዳግም ለመቀስቀስና ምዕመኑን ወደማያባራ ቀውስ ውስጥ ለመክተት በማሴር እነ ያሬድ አደመ ስራቸውን እየሰሩ ይገኛሉ ፤ ቅዳሴ ቤተክርስትያን እያስቀደሱ ወንጌሉን ደግሞ በአዳራሽ የሚል ፈሊጥ በመያዝ ለተግባራዊነቱ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ፤ ውስጦቻችን ተሰግስገው ያሉ አመቺ ጊዜ የሚጠብቁ ሰዎች ተበራክተዋል ፤ አሁንም በአንድም ይሁን በሌላ መንገድ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን እና መናፍቃኑ አዳራሽ የሚመላለሱ ሁለቱም ጋር የሚያገለግሉ ሰዎች ተበራክተዋል ፤ በተመሳሳይ አንዳንድ ከተማዎች ላይ የቅባት እና የጸጋ አስተምህሮ ያላቸው ሰዎች ምዕመኑን እያመሱት ይገኛሉ ፤ ከነዚህ በተጨማሪም አሁን የማናመላክተው  በርካታ ነገሮችም አሉ ፤ እነዚህ ሁሉ ጉዳዮች ወደፊት ጊዜውን ጠብቀው የሚፈነዱ ቦምቦች ናቸው ፡፡

ስለዚህ ማንም የድብቅ ሸንጎ በመጥራት እኛ ላይ ብሎጋችንን ለማዘጋት ቢያሴሩ ፤ ከቤተክህነት በቀጥታ ለመንግስት ብሎጎቹ እንዲዘጉ ደብዳቤ ቢጻፍ ፤ መንግስትም ከራሱ ፍላጎት በመነሳት በሌላ አይን በመመልከት ብሎጋችንን ቢዘጋ ፤ እኛ ግን ከመጻፍ ወደ ኋላ የሚገታን አንዳች ነገር አይኖርም ፤ እነርሱ ለመዝጋት ካልደከማቸው እኛ አዲስ ለመክፈት አይሰለቸንም ፤ አፍራሽ ግብረ ሃይሎችን አይተን ዝም የምንልበት አይን ሰምተን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለን የምናልፍበት ጆሮ የለንም ፤  ጽሁፎቻችን ዋልድባ ከሚገኙ መነኮሳት ጀምሮ በተለያዩ ሀገሮች ድረስ ተደራሽ መሆን ችሏል ፤ ቀድሞ በቀን ከ5ሺህ ሰዎች በላይ ቢጎበኙንም አሁን ብሎጉ ተዘግቶ ቢያንስ በቀን መረጃውን ከ3ሺህ በላይ ሰዎች ጋር ስለምናደርስ ተስፋ ባለመቁረጥ እንሰራለን፡፡

ቸር ሰንብቱ

“በጸሎታችሁ አስቡኝን ይመለከታል” የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ

በተጨማሪ ሁለት ገጾችን ኢትዮጵያ ውስጥ ለመነበብ እንሞክራለን

(አንድ አድርገን ሐምሌ 25 2004 ዓ.ም)፡- በቀደምት ዘመናት ኢትዮጵያን ሲያስተዳድሩ የነበሩ ነገስታት ሀገራቸው ላይ የተለያዩ ችግሮች በሚፈጠሩበት ጊዜ በየአህጉረ ስብከት ውስጥ የሚገኙ ገዳማት እና አድባራት “በጸሎታችሁ አስቡን” ፤ “በጸሎታችሁ አትርሱኝ” የሚል ደብዳቤ እንደሚጽፉ የታሪክ መዛግብት ይናገራሉ  ፡፡በጊዜው በቅርብም ሆነ በሩቅ ላሉ ገዳማትና አድባራትም “አትርሱኝ” እየተባለ ይነገራል ፤ ይጻፍላቸዋልም ይህንኑም አጥብቀው ለህዝቡ እና ለአባቶች  ማሳወቅ ጠቃሚ ስለሆነ በንጉሰ ነገስቱ ማህተም እየታተሙ ወደ ተለያዩ ገዳማት ይላካሉ ፤ በጊዜው ከተላኩት ደብዳቤዎች ለማስረጃ ያህል የሶስቱን ግልባጭ ከዚህ ቀጥለን ለማሳየት እንሞክራለን….

ጊዜው ድርቅ ሆኖ ለሰብል የሚያሰጋ በመሆኑ

 ዐዋጅ

ባለፈው ዘመን ሰብል መታጣት ስናዝን ይህው ዘንድሮም ጊዜው እንዳምናው ለመሆን የሚያሰጋ ሆኗልና አሁን ስለ ድርቁም ወደ እግዚአብሔር እንዘን፡፡ መስኖም እያወጣህ እህል ዝራ ፤ አታክልት ትከል ፤ ዳኝነትና ውርርድ ፤ ሰማኒያ ፤ የስድብ መቀጫ የገባውንም የተሰደበውንም ሰው ከሚካሰው ካሳ በቀር እስከ መጋቢት ሥላሴ ያለውን ምረናልና መኳንንቱም ሹማምንቱም ማርልን፡፡

መጋቢት 20 ቀን 1920 ዓ.ም መጋቢት 15 ቀን ተጻፈ

ሰንበትን በግዝት የተከለከለውን በዓል ስለማክበር

 
ዐዋጅ
በሰንበትና በግዝት በተከለከለው በዓል ቀን ሥራ እንዳይሰራ ተብሎ ከዚህ ቀደም ብዙ ጊዜ ዐዋጅ ተነግሮ ተከልክሎ ነበር ፤ አሁን ግን በተከበረው በዓል ቀን ይልቁንም ዕለተ ሰንበትን በመድፈርና ግዝትንም በመድፈር ፤ ግዝትም ዐዋጅም ጥሰህ ስራ እየሰራህ በዚህ ምክንያት በየጊዜው መቅሰፍቱ አልታገስ አለን፡፡ አሁንም ሰንበትንና ከዚህ ቀደም የተከለከለውን በዓል አክብር ፤ በተከለከለውም በዓል ቀን ስራ አትስራ ፤ በዚህ በግዝትና ባዋጅ በተከለከለው በዓል ቀን ሲሰራ የተገኝ ሰው ይቀጣል፡፡
ሀምሌ 16 ቀን 1920 ዓ.ም

ስለ ዘውድ በዓል አትርሱኝ

ሞአ አንበሳ ዘእምነገደ ይሁዳ
ቀዳማዊ ኃይለስላሴ
ሥዩመ እግዚአብሔር ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ
ይድረስ፡-
እግዚአብሔር ከስጋ ከምወለዳቸው ከቃል ኪዳን እናቴ ወደ ኋላ አስቀርቶ የንጉሰ ነገስቱን ወራሽ ስላደረገኝ የዘውዱን በዓል ለማክበር አስቤ አለሁና በንጉሰ ነገስትነት በሚሰራ ስራ ሁሉ እሱ እግዚአብሔር  ሰሪ ሆኖ መሳሪያ እንዲያደርገኝ ከዛሬ ዠምራችሁ እስከ ዘውዱ በዓል ድረስ በጸሎት ምልጃችሁን ወደ እግዚአብሔር እንድታመላክቱኝ አትርሱኝ ብዬ እለምናችኋለሁ
1922 ዓ.ም ተጻፈ
ይህ ታሪክ የሚያሳየን እውነታ ቢኖር በዘመናት ይችን ሀገር እንደ አምላክ መልካም ፍቃድ ያስተዳደሯት ገዥዎቻችን ሀገር በእርዛት ፤ በርሀብ ፤ በዝናብ እጦት በችግር እና በጦርነት ስትወጠር በየአህጉረ ስብከቶች ያሉ ገዳማትና አድባራት ጋር “በጸሎታችሁ አትርሱኝ” የሚል ደብዳቤ እንደሚልኩ ማሳያ ነው ፤ ከዚህም በተጨማሪ እግዚአብሔር ምህረቱን እንዲያወርድላቸው ጸሎታቸውን እንዲሰማላቸው በእስር የሚገኙ ታራሚዎችን የመልቀቅ ልማድም ነበር ፤ ከታሪክ ጠቃሚውን ወስደን የማይጠቅመውን ብናስወገድ መልካም ይመስለናል ፤ አሁንም ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትሯ ህመም የተነሳ ውጥረት ውስጥ ትገኛለች ፤ በዚህ ጊዜ መንግስት ይህን መልዕክት ለገዳም አባቶች ቢልክ ምን ይመስሎታል?

 

ጉዳዩ ፡- በጸሎታችሁ አስቡኝን ይመለከታል

 ለ፡- ዋልልድባ ገዳም ማህበረ መነኮሳት

 እንደሚታወቀው ላለፉት 21 ዓመታት ይችን ሀገር በጠቅላይ ሚኒስርነት መምራቴ ይታወቃል ፤ ከዚህ በፊት በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ስላደረስኩባችሁ በደል አባቶቼ ሆይ ይቅር በሉኝ ፤ ሆኖም በአሁኑ ሰዓት በያዘኝ የጭንቅላት ህመም አልጋ ላይ ከጣለኝ ይህው ዛሬ 42ተኛ ቀኔን ቆጥሬአለሁ ፤ በዚች አጭር ጊዜ እግዚአብሔር ቸርና መሐሪ፥ ቍጣው የዘገየ፥ ምሕረቱም የበዛ አምላክ መሆኑን አውቄአለሁ ፤ እግዚአብሔር ምህረቱን እንዲልክልኝ በጸሎታችሁ እንድታስቡኝ ወደ እግዚአብሔር እንድታመለክቱልኝ አትርሱኝ ብዬ እለምናችኋለሁ፡፡
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
መለስ ዜናዊ..   
ሐምሌ 25 2004 ዓ.ም ተጻፈ
ቸር ሰንብቱ
ግብዓት፡- ከመጽሀፈ ዝክረ ነገር (ከብላቴ ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል)

እረ ጉድ ነው

(አንድ አድርገን ሐምሌ 24 2004 ዓ.ም)፡- በአሁኑ ጊዜ የማይሰማ ነገር የለም ፤ በየቦታው የሚሰማው ነገር ጆሮን ጭው የሚያደርጉ ነገሮች እየሆኑ ለመስማትም ሆነ ለመጻፍ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ እንገኛለን ፤ የዛሬ 6 ወር ገደማ “እኔ እየሱስ ክርስቶስን የምወልደው ሴት ነኝ” ብላ የተነሳች ሴት መከሰቷን በጊዜው በቦታው ተገኝተን በአይናችን ካየነው ፤ በጆሯችን ከሰማነው ፤ ከጋዜጦች ካነበብነው እና ከፖሊስ መረጃ ጋር በማመሳከር አንድ ጽሁፍ ማቅረባችን ይታወሳል ፤ በጊዜው የተከሰተችው ሴት ከዚህ በፊት ተሰምቶም ሆነ ታይቶ የማይታወቅ ተግባር ስለፈጸመች ብዙዎችን ጉድ አሰኝታ ነበር ፤ ከሰማይ የወረደ  መና ነው በማለት ብዙዎችን ምንነቱ ያልታወቀ ምግብ አብልታቸዋለች ፤ ይህ ሁሉ ሲደረግ ስለ እሷ ሽንጣቸውን ገትረው የሚከራከሩ ብዙ ነጫጭ የለበሱ ሴቶችን አስከትላ ገድሏን ሲመሰክሩላት ሲመለከቱ ይህ ነገር ህልም እንጂ እውን አይመስሎትም ፤ እኛ ከተደረጉት ነገሮች ሁሉ ለእናንተው ጆሮ ለዘብ ያለውን ጉዳይ ብቻ አቅርበናል ፤ ይች ሴት የተነሳችበት ዓላማ በጣም አደገኛ ከመሆኑ የተነሳ ብዙዎችን “እኔ እግዚአብሔር የመረጠኝ ክርስቶስን የምወልደው ሴት ነኝ” በማለት በቤተክርስትያን ውስጥ በርካቶችን ያወዛገበች ፈት ሴት መሆኗን ለማወቅ ተችሏል ፤  በአዲስ አበባ አስኮ መንገድ የሚገኝው የአባታችን የአቡነ ሐብተማርያም ቤተክርስትያን በበአላቸው ቀን በመገኝት አውደ ምህረት ላይ በመውጣት ስትናገር የነበረው ነገር በርካታ ወጣቶችን በማስቆጣቱ ከፍተኛ ችግር መፈጠሩ የሚታወቅ ነው ፤ በጊዜው ያልተገባ ነገር ስትናገር የሰሙ ወጣት ምዕመናን ከአውደ ምህረት ላይ ውረጂ ሲሏት ባለመስማቷ አንጠልጥለው ሊያወርዷት ወደ አውደ ምህረቱ ሲያመሩ የሚመጣውን ጉዳት ከግምት በማስገባት ተሸቀንጥራ በግብር አበሮቿ አማካኝነት በመታጀብ  ቤተክርስቲያኑ ጎን  የሚገኝው መሰብሰቢያ አዳራሽ በመግባት ከተቆጡት ወጣቶች ማምለጥ ችላለች ፤  ይህ በእንዲህ እያለ በአዳራሽ ውስጥ አብረዋት የገቡት ግብር አበሮቿ ፖሊስ ዘንድ በመደወል ከሚደርስባት ጉዳት ሊያድኗት ችለዋል ፤ በጊዜው የነበሩ ወጣቶች ሁኔታውን ሲያስረዱ ስለ ቤተክርስቲያንና በድፍረት በአውደ ምህረት ላይ ስለተናገረችው ቃል እንባ እየተናነቃቸው ምግባሯንና ያደረገችውን ነገር መናገርና መግለጽ እስኪያቅታቸው ድረስ ደርሰው ነበር ፡፡

Read the rest of this entry